| ከኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር የተሰጠ መግለጫ - Page 2 |
|
|
|
| Written by Administrator | ||||
| Wednesday, 07 April 2010 18:19 | ||||
Page 2 of 2
Email – This e-mail address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it website- www.arbegnochginbar.com
የኢህአግ ሰራዊት በወያኔ ላይ እየወሰደ ያለውን ወታደራዊ የማጥቃት እርምጃ ከእስካሁኑ በላቀ ሁኔታ ወያኔው የሚመካበትን የታጠቀ የግፍ ሃይል ለማንኮታኮት እየሰራ ይገኛል። በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ወያኔን ለማስወገድ በሚካሄደው እንቅስቃሴ ቀላል የማይባል ሚና ተጫውተዋል። ይሁን እንጅ ተሳትፉቸውንና ጥረታቸውን በማዋሃድና አንድ አቅጣጫ በማስያዝ ረገድ በርካታ ሙከራዎች የተደረጉ ቢሆንም የተፈለገውን ያህል ውጤት አላስገኘም። ድርጃታችን ኢ.ህ.አ.ግ ይህን በመረዳት ከውጭ በተመረጡ ማእከላዊ ኮሚቴ አባላትና ከነሱም መካከል በሰብሳቢው በምክትል ሰብሳቢው እና በዋና ፀሃፊው አስተባባሪነትና አመራር ሰጭነት ሲሆን 14ቱ የማእከላዊ ኮሚቴ አባላትና ሌሎች ነዋሪነታቸውን በውጭ ያደረጉ ወገኖች ሁሉ በተመቻቸው አንድ ወጥ መንገድ ስር በመሰባሰብ እና የሚሰጠውን አገራዊ ተልእኮ በመፈፀምና በማስፈፀም አገርና ህዝብን እያወደመ የሚገኘውን አንባገነኑን የወያኔ ቡድን ይበቃል ልንለው ይገባል። በተለያየ መንገድ በኢ.ህ.አ.ግ ስም ይንቀሳቀሱ የነበሩ ቡድኖች ህዝብን ከማወናበድ ተግባር ተቆጥበው በተመቻቸው መንገድ ውስጥ ገብተው እንዲንቀሳቀሱና በጉባኤው በተላለፈው ውሳኔ መሰረት arbegnochginbar.com ውጭ በኢህአግ ስም የተከፈቱ ድረ- ገፆች ህገ-ወጥ መሆናቸውን እያሳወቅን ድርጅታችን በወታደራዊ በፖለቲካና በዲፕሎማሲ… ያለውን ሃይል በመጠቀም ተግቶ ይሰራል። ወያኔው እየተዘጋጀለት የሚገኘውን የይስሙላ ምርጫ ምእራባውያንም ቢሆኑ እውነታውን የተገነዘቡበትና ፊታቸውን ያዞሩበት ወቀት በመሆኑ በዚህ አጋጣሚ ኢትዮጵያዊ የሆንን ወገኖች ሁሉ ጎጠኛውን አገዛዝ ከስር መሰረቱ ለማስወገድ የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር አንድ አካል ሆነን አገራችን ኢትዮጵያን ከገባችበት አዘቅት ልናወጣት ይገባል።
አንድነት ሃይል ነው!!! የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር
መጋቢት 20 ቀን 2002 አ/ም |
||||
| Last Updated on Friday, 11 March 2011 14:20 |
Search
Latest Articles
-
10-09-2005
(1999-11-30 00:00:00) -
08-09-2005
(1999-11-30 00:00:00) -
06-09-2005
(1999-11-30 00:00:00) -
03-09-2005
(1999-11-30 00:00:00) -
01-09-2005
(1999-11-30 00:00:00)


ስለ ኢሕአግ


